የግል ድርጅት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር ስትራቴጅክ ዕቅድ (2016-2018)
የግል ድርጅት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር ስትራቴጅክ ዕቅድ (2016-2018)
አገልግሎቶቻችን
የድርጅቶች ምዝገባ:-
በሀገሪቱ ከሚገኙት አንድና ከዛ በላይ ሰራተኞችን ቀጥረው የሚያሰሩ የግል ድርጅቶች ፣ድርጅታቸውንና ሰራተኞቻቸውን እንዲያስመዘግቡ እየተደረገ ሲሆን ድርጅታቸውንና ሰራተኞቻቸውን ያላስመዘገቡ ይግል ድርጅቶች የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መንገዶችን በመጠቀም እንዲያስመዘግቡ እየተደረገ ይገኛል።
የሰራተኞች ምዝገባ:-በሀገራችን ውስጥ ባሉ የግል ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው ሰራተኞችን ሙሉ በሙሉ የአቅድ አባልነት ምዝገባ ማካሄድና መረጃቸውን ማደራጀት።
የግል ድርጅቶች በግል ድርጅቶች ውስጥ ከ45 ቀናት ላላነሰ ግዜ ደሞዝ እየተከፈለው ለተወሰነ ወይይም ላልተወሰነ ግዜ ወይም የተወሰነ ስራ ለመስራት ከተቀጠረ ሰራተኛ የሰበሰበውን የጡረታ መዋጮ እና የራሱን ድርሻ ጨምሮ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን እና የክልል የገቢ/የስራ ግብር ሰብሳቢ ተቋማት ግብርና ታክስ በሚሰበሰብበት ስርዓት / መንገድ ደሞዝ በተከፈለበት ወር ቀጥሎ ባለው 30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የጡረታ መዋጮ ማሳወቂያ ቅፅ በሚጠይቀው መሰረት በመሙላትና በሚመለከተው የስራ ኃላፊ ፊርማ ና ማህተም በማድረግ ለተቋሙ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል።
አስተዳደሩ ከተቋቋመ አንስቶ በእድሜ፣በጤና ጉድለት በስራ ላይ ጉዳት ፣ በዋና ባለመብትና በሞት በተተኪዎች ላይ የሚደርሰውን የገቢ ማቋረጥ በመተካት የጡረታ አበል በመወሰንና የአቅዱ አባል ለነበሩና በጡረታ ለተገለሉ የግል ድርጅት ሰራተኞች እንዲሁም በሞት ለተለዩ የአቅዱ አባላት ቤተሰቦች የጡረታ አበል በመክፈል ላይ ይገኛል።የአንድ ግዜ /ዳረጎት ክፍያን ሳይጨምር ለበርካታ ዋና ባለመብትና ተተኪዎች የሟች ሚስት/ባል ፣ልጆችና ቤተሰቦች ክፍያ በመፈፀም ሀገሪቱ በምታደርገው የድህነት ቅነሳ ላይ የራሱን አሻራ እያሳደረ ይገሻል።
የተቀናጀ
መከታተያ ስትዓት
አሰባሰብ ስርዓት
ፈጣንና ቀልጣፋ የጡረታ አበል አከፋፈል ስርዓት
የተቀናጀ የመረጃ አያያዝ ስርዓተ
Recent Updates
የግል ድርጅት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር ስትራቴጅክ ዕቅድ (2016-2018)
ድርሞ /Excutive summary/
አስተዳደሩ የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ፡፡
አዲሱ የማህበራዊ ዋስትና አዋጅ